Skip to main content

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አመራር አካዳሚ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር "የመረጃ ትንተና ክህሎት ለአገልግሎት ልህቀት" በሚል መሪ ቃል በሳጃ ከተማ ስልጠና መስጠት ጀመረ! ሳጃ:- ሚያዝያ 13/2018

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አመራር አካዳሚ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር "የመረጃ ትንተና ክህሎት ለአገልግሎት ልህቀት" በሚል መሪ ቃል በሳጃ ከተማ ስልጠና መስጠት ጀመረ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አመራር አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ብላቱ በስልጠናው መክፈቻ ወቅት እንደገለጹት

አካዳሚው በአዋጅ ሁለት ተልዕኮ ተሰጥቶት የተቋቋመ ሲሆን አንደኛው ስልጠና 2ተኛው የጥናትና ምርመር ተልዕኮ እንደሆነ ገልጸው ከዚህ ተልዕኮ በመነሳት ለ24 ሰዓት ክልላችንን ሰለማዊና የተረጋጋ ክልል ለማድረግ ለሚተጉ በየደረጃው ለሚገኙ የፖሊስ አመራሮች እውቀት ሊጨመር፤ የተሻለ ግንዛቤ ሊፈጥር የሚችል ስልጠና መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ቢሮው ስልጠናውን አዘጋጅቷል ብለዋል፡፡

በዘመናችን መረጃዎች በፍጥነት እየተቀያየሩና እየተለዋወጡ ነው ያሉት አቶ ተስፋዬ፤ ለዚህም ከፍተኛ የሆነ እውቀት፣ ክህሎት እና የቴክኖሎጂ አቅም ማሳደግ ይጠይቃል ስሉ አስገንዝበዋል። 

ኃላፊው አያይዘውም ሰልጣኙ ከዚህ ስልጠና የሚያገኘው እውቀት በክፍል ውስጥ ብቻ የሚቆይ ሳይሆን በተግባር ላይ በሚፈጸሙ ስራዎች ላይ በቀጥታ የሚተገበር እንደሆነም ገልጸው ሰልጣኞች በዚህ መሠረት ስልጠናውን በንቃት እንድሳተፉ መመሪያ ሰጥቷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አመራር አካዳሚ ም/ዋና ደይሬክተር አቶ አቢቲ ኢንሴቦ በበኩላቸው ስልጠናው እየተሰጠ ያለው በሁለት ዋና ዋና ርዕሰ ጉደዮች ማለትም የወንጀል መረጀ ትንተና እና የወንጀል ስታትስቲክስ ሪፓርት አዘገጃጀት ክህሎት ዙሪያ ሲሆን ይህም ፖሊሶች በእለት ተእለት ስራዎች በመረጃ የተመሠረቱ እና በሳይንሳዊ መንገድ የሚመራ ስራ እንዲሰሩ ያግዛል፤ ይህም በሂደቱ የወንጀል መቀነስን እና በተቋሙ ላይ የህዝብ አማኔታ(public trust ) እንድጨምር ያደርገል ብለዋል ።

አክለውም ስልጠናው አመራር አካዳሚው ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር " የወንጃል መረጃ ትንተና ክህሎት ለአገልግሎት ልቀት" በሚል መሪ ቃል ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ 4 ቀን የሚቆይ እንደሆነም ገልጿል።

በስልጠናው መድረክ ላይ የአመራር አካዳሚው ኃላፊዎች፣የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኃላፊዎች፣የቢሮው ማኔጅመንት አካላት፣ ከሁሉም ዞን፣ልዩ ወረዳ፣እንደውም ከተማ አስተዳደር ከፖሊስ መዋቅር የተመለመሉ ሰልጣኝ የፖሊስ አካላት ተገኝቷል።

Image
Photo of Ato Tesfaye Bilatu